1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኢትዮጵያ ህዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ የወደፊት እቅድ

ሰኞ፣ መስከረም 14 2011

የኢትዮጵያ ህዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ፣ ኢህአፓ ከ46 ዓመት በኋላ ባለፈው የሳምንት መጨረሻ አዲስ አበባ ገብቷል። ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አህመድ በውጪ ያሉ የተለያዩ ፖለቲካ ፓርቲዎች ለአገር ግንባታ ወደ አገር እንዲገቡ ያደረጉትን ጥሪ ተከትሎ ነው ከፍተኛው የፓርቲው አመራር ቡድን ሰሞኑን ወደ ሀገር የተመለሰው።  

Karte Äthiopien englisch

ኢህአፓ

This browser does not support the audio element.

ከአራት አሰርተ ዓመት በላይ በኋላ ወደ ሀገር ቤት የተመለሰው ኢህአፓ በአጭር ጊዜ እቅዱ መሰረት በዓብዮቱ ጊዜ ከኢህአፓ ጋር በተያያዘ ይሰሩ ከነበሩ ህዝባዊ ድርጅቶች ጋር ሲንቀሳቀሱ ጉዳት የደረሰባቸውን አፈላልጎ የችግራቸው ተካፋይ መሆኑን ለመግለጽ እና ለተሰሩ ስህተቶችም ይቅርታ ለመጠየቅ እንደሚፈልግ የከፍተኛው ቡድን መሪ አቶ ማስረሻ ዮሴፍ ለDW ገልጸዋል። በመካከለኛ ጊዜም ፓርቲው ከህብረተሰቡ ጋር በዓላማ እና በፖለቲካ ላይ የተመሰረተ ውይይት እያካሄደ የፖለቲካ ስራውን የመጀመር እቅድ እንዳለውም አቶ ማስረሻ አክለው አስታውቀዋል።

ገበያው ንጉሤ

አርያም ተክሌ

ሸዋዬ ለገሠ

 

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW